Thursday, October 16, 2008

Elias Kifle on Hailu Shawel's house in Addis up for rent

Hailu Shawel's house in Addis up for rent
http://www.ethiopianreview.com/content/1706
http://www.zikkir.com/zena/?p=99
January 4th, 2008 | 6 Comments
The estranged chairman of Kinijit has put up his huge house in Addis Ababa for rent. The asking monthly rate is $6,500 USD (60,000 birr). This has intensified the speculation that Ato Hailu will not return to Ethiopia
የኃይሉ ሻውል መመለስ አጠራጣሪ ሆኗል
አምስት የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ የስራ አስፈጻሚ አባላትን ከፓርቲው ህገ ደንብ ውጭ አግጃለሁ በማለት ህዝባዊው ድርጅት በገዢው ፓርቲ እየተፈጸመበት የነበረውን የማፍረስ ጥረት ከፍተኛ እገዛ የሰጡት ኃይሉ ሻውል ወደ አገር ቤት የመመለሳቸው ጉዳይ አጠራጣሪ መሆኑን የቅርብ ምንጮች አመለከቱ፡፡
ሊቀ መንበሩን መመለስ ከሚጠራጠሩት ወገኖች አንደኛው በቀድሞው የመኢአድ ጽ/ቤት በመሆን የአቶ ኃይሉን ትእዛዝ የሚያስፈጽሙት አባላት ጭምር መሆናቸው ጉዳዩን አስገራሚ አድርጎታል፡፡ በጽ/ቤቱ በሚደረጉ የውይይት አጀንዳዎች ላይም ይህ ሃሳብ ተነስቶ እንደማያውቅ ማንነታቸው እንዲገለጽ ያለፈለጉ የቅርብ ወዳጆቻቸው ገልጸዋል፡፡
በተለይ ሰሞኑን ሳሪስ አቦ የሚገኘውን የአቶ ኃይሉን ቤት ለማከራየት በደላሎች አማካይነት እየተደረገ ያለው ጥረት አቶ ኃይሉ መኖርያቸውን በዘላቂነት በአሜሪካ ሊያደርጉ ይችላሉ የሚለውን ጥርጣሬ አጉልቶታል፡፡ለዚህ የመኖርያ ቤት የተጠየቀው የኪራይ መጠን 60 ሺህ ብር (U.S. $6,500 በወር) ያህል መሆኑን የተከራይ አፈላላጊዎቹ ገልጸውልናል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓርቲውን ሃላፊነት ተረክቦ ወሳኝ እንቅስቃሴዎችን የጀመረው የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ አካል በእሁዱ ላእላይ ም/ቤት አባላት የተላለፉትን ውሳኔዎች ለማስፈጸም ከፍተኛ እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በትናንትናው እለት በመሰብሰብ በተግባራዊ ሂደቶች ዙርያ በሚያከናውናቸው አጀንዳዎች ዙርያ መክሯል፡፡

No comments: